top of page

የኮቪድ-19 ገደብ ተላልፈው ሲጨፍሩ የነበሩ 13 ወጣቶች ሞቱ

በላቲን አሜሪካዋ አገር ፔሩ ነው ይህ አሳዛኝ ክስተት የተፈጸመው፡፡

በአንድ መሸታ ቤት በር ዘግተው የልደት ድግስ አሰናድተው፣ "አስረሽ ምቺው" ላይ የነበሩ ወጣቶች ፖሊስ ይደርስባቸዋል፡፡

በፖሊስ መከበባቸውን ሲያውቁ በመሸታ ቤቱ አንዲት ቀጭን በር በኩል ለማምለጥ ሩጫ ይጀመራል፡፡

በዚህ ጊዜ ነው መረጋገጥና መተፋፈግ ተፈጥሮ ለሳቅ ለጨዋታ እንዲሁም ለደስታ የመጡ 13 ሰዎች ሕይወት እንዲህ እንደዋዛ ያለፈው፡፡

ፖሊስ ድንገተኛ ወረራ ያደረገው ጥቆማ ደርሶት ነው፡፡

በኮቪድ-19 ምክንያት ሰዎች ተሰብስበው እንዳይጨፍሩ የፔሩ መንግሥት እገዳ ከጣለ ሰነባብቷል፡፡

በሊማ፤ ሎስ ኦሊቮስ በሚባለው ሰፈር ቶማስ ሬስቶባር ናይት ክለብ ነው ይህ አሳዛኝ አደጋ የደረሰው፡፡




የአይን እማኞች እንደሚሉት ፖሊስ አስለቃስ ጭስ ተጠቅሟል፡፡ ፖሊስ በበኩሉ እኔ አልተኮስኩም ሲል ተከራክሯል፡፡

ፕሬዝዳንት ማርቲን ቪዝካራ እንደተናገሩት በመሸታ ቤቱ ውስጥ አሸሼ ገዳሜ ሲሉ ከነበሩና ምርመራ ከተደረገላቸው 23 ወጣቶች ውስጥ 15ቱ ተህዋሲው ተገኝቶባቸዋል፡፡

ፔሩ ከደቡብ አሜሪካ አገሮች ውስጥ ኮቪድ ክፉኛ ካጠቃቸው ተርታ ትመደባለች፡፡ ግማሽ ሚሊዮን ሰዎች ተህዋሲው የያዛቸው ሲሆን 27ሺ ሰዎች ሞተዋል፡፡

ይህን ተከትሎ ነው ካለፈው መጋቢት አጋማሽ ጀምሮ ሰአት እላፊ የታወጀው፡፡

የፔሩ የአገር ውስጥ ሚኒስትር እንዳሉት የቅዳሜውን የልደት ድግስ 120 ሰዎች ታድመውበት ነበር፡፡

በጭፈራ ላይ የነበሩት ወጣቶች ፖሊስ መምጣቱን ሲያውቁ በደረጃው ላይ ቀድመው ለማምለጥ ሙከራ ላይ በነበሩበት ጊዜ ነው መጨፈላለቁ ተፈጥሮ አደጋው ሊደርስ የቻለው፡፡

ከ13ቱ ሟቾች ውስጥ ሁለቱ ሴቶች ናቸው፡፡

የመሸታ ቤቱ ባለቤት የሆኑት ባልና ሚስት ለጊዜው በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡

 
 
 

Comments


Post: Blog2_Post

GH ETHIO NEWS.COM

Your Go-To Source

We are all told, “live your life to the fullest”; I am here to do just that. GH ETHIO NEWS.COM serves as a vessel to project my passions, and clue in my loyal readers as to what inspires me in this crazy world. So, sit back, relax, and read on.

Post: Welcome

Subscribe Form

Thanks for submitting!

0936323517

©2020 by GL NEWS AMHARIC.COM. Proudly created with Wix.com

bottom of page